4. የመዝሙረኛው ቃሉን የመታዘዝ ህይወት Obeying the Word

Sermon  •  Submitted   •  Presented
0 ratings
· 5 views
Notes
Transcript
1 በመንገዳቸው ንጹሐን የሆኑ በእግዚአብሔርም ሕግ የሚሄዱ ምስጉኖች ናቸው።
2 ምስክሩን የሚፈልጉ፥ በፍጹም ልብ የሚሹት ምስጉኖች ናቸው፤
3 ዓመፅንም አያደርጉም፥ በመንገዶቹም ይሄዳሉ።
4 ትእዛዛትህን እጅግ እንጠብቅ ዘንድ አንተ አዘዝህ።
5 ሥርዓትህን ለመጠበቅ፤ መንገዶቼ ይቀኑ ዘንድ እወድድ ነበር።
8 ሥርዓትህን እጠብቃለሁ፤ በፍጹም አትጣለኝ። ቤት
9 ጕልማሳ መንገዱን በምን ያነጻል? ቃልህን በመጠበቅ ነው።
10 በፍጹም ልቤ ፈለግሁህ፥ ከትእዛዝህ አታርቀኝ።
11 አንተ እንዳልበድል፥ ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።
17 ለባሪያህ መልካም አድርግ ሕያው እንድሆን፥ ቃልህንም እንድጠብቅ።
18 ዓይኖቼን ክፈት፥ ከሕግህም ተኣምራትህን አያለሁ።
55 አቤቱ፥ በሌሊት ስምህን አሰብሁ፥ ሕግህንም ጠበቅሁ።
56 ትእዛዛትህንም ፈልጌአለሁና፤ ይህች ሆነችልኝ። ሔት
57 እግዚአብሔር ክፍሌ ነው፤ ሕግህን እጠብቃለሁ አልሁ።
60 ትእዛዝህን ለመጠበቅ ጨከንሁ አልዘገየሁምም።
61 የኃጥኣን ገመዶች ተተበተቡብኝ፤ ሕግህን ግን አልረሳሁም።
63 እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፥ ትእዛዝህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ።
67 እኔ ሳልጨነቅ ሳትሁ፤ አሁን ግን ቃልህን ጠበቅሁ።
80 እንዳላፍር ልቤ በሥርዓትህ የቀና ይሁን። ካፍ
81 ነፍሴ መድኃኒትህን ናፈቀች፤ በቃልህም ታመንሁ።
87 ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም።
88 እንደ ምሕረትህ ሕያው አድርገኝ፤ የአፍህንም ምስክር እጠብቃለሁ። ላሜድ
89 አቤቱ፥ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል።
100 ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋልሁ።
101 ቃልህን እጠብቅ ዘንድ ከክፉ መንገድ ሁሉ እግሬን ከለከልሁ።
102 አስተምረኸኛልና ከፍርድህ አልራቅሁም።
104 ከትእዛዝህ የተነሣ አስተዋልሁ፤ ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ጠላሁ። ኖን
105 ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።
106 የጽድቅህን ፍርድ እጠብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸናሁም።
107 እጅግ ተቸገርሁ፤ አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ሕያው አድርገኝ።
110 ኃጢአተኞች ወጥመድን ዘረጉብኝ፤ ከትእዛዝህ ግን አልሳትሁም።
111 የልቤ ደስታ ነውና ምስክርህን ለዘላለም ወረስሁ።
112 ለዘላለም ለፍጻሜውም ትእዛዝህን አደርግ ዘንድ ልቤን አዘነበልሁ። ሳምኬት
113 ዓመፀኞችን ጠላሁ፥ ሕግህን ግን ወደድሁ።
128 ስለዚህ ወደ ትእዛዝህ ሁሉ አቀናሁ፥ የዓመፅንም መንገድ ሁሉ ጠላሁ። ፌ
129 ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው።
133 አካሄድን እንደ ቃልህ አቅና፤ ኃጢአትም ሁሉ አይግዛኝ።
134 ከሰው ግፍ አድነኝ፤ ትእዛዝህንም እጠብቃለሁ።
135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፥ ሥርዓትህንም አሰተምረኝ።
136 ሕግህን አልጠበቅሁምና የውኃ ፈሳሽ ከዓይኖቼ ፈሰሰ። ጻዴ
145 በፍጹም ልቤ ጮኽሁ፥ አቤቱ፥ ስማኝ፤ ሥርዓትህን እፈልጋለሁ።
146 ወደ አንተ ጮኽሁ፤ አድነኝ፥ ምስክርህንም እጠብቃለሁ።
147 ማለዳ ጮኽሁ፤ ቃልህንም ተስፋ አድርጌአለሁ።
157 ያሳደዱኝና ያስጨነቁኝ ብዙዎች ናቸው፤ ከምስክር ግን ፈቀቅ አላልሁም።
158 ቃልህን አልጠበቁምና ሰነፎችን አይቼ አዘንሁ።
166 አቤቱ፥ ማዳንህን ተስፋ አደርግሁ፥ ትእዛዛትህንም ጠበቅሁ።
167 ነፍሴ ምስክርህን ጠበቀች እጅግም ወደደችው።
168 መንገዶቼ ሁሉ በፊትህ ናቸውና ትእዛዝህንና ምስክርህን ጠበቅሁ። ታው
5.ቃሉን መናገር / Proclaiming the Word
13 የአፍህን ፍርድ ሁሉ በከንፈሬ ነገርሁ።
42 በቃልህ ታምኛለሁና ለሚሰድቡኝ በነገር እመልስላቸዋለሁ።
43 በፍርድህም ታምኛለሁና የእውነትን ቃል ከአፌ ፈጽመህ አታርቅ።
46 በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም፤
54 በእንግድነቴ አገር ሥርዓትህ መዝሙር ሆነችኝ።
108 አቤቱ፥ ከአፌ የሚወጣውን ቃል ውደድ፥ ፍርድህንም አስተምረኝ።
172 ትእዛዛትህ ሁሉ ጽድቅ ናቸውና አንደበቴ ቃልህን ተናገረ።
Related Media
See more
Related Sermons
See more
Earn an accredited degree from Redemption Seminary with Logos.