ብተና የማያግደው ወንጌል - የሐዋርያት ሥራ 8:1-8

Sermon  •  Submitted
0 ratings
· 125 views

ቤተ ክርስቲያን በማንኛውም በታኝ ኃይል ስትገፋ አማኞች በጸሎትና በቃሉ ሲተጉ፣ በውስጧ ድንቅና ተአምር፣ የመንፈስ አንድነትና፣ በውጭ ለህዝብም ደስታ ምክንያት ትሆናለች።

Notes
Transcript

ብተና የማያግደው ወንጌል

ቤተ ክርስቲያን በማንኛውም በታኝ ኃይል ስትገፋ አማኞች በጸሎትና በቃሉ ሲተጉ፣ በውስጧ ድንቅና ተአምር፣ የመንፈስ አንድነትና፣ በውጭ ለህዝብም ደስታ ምክንያት ትሆናለች።

“ከምድር ሊያጠፉኝ ጥቂት ቀርቶአቸው ነበር፤ እኔ ግን ትእዛዛትህን አልተውሁም።” መዝሙረ ዳዊት 119፥87

መግቢያ፥

አማኝን ሊበትን የሚመጣ ስደት አይቀሪ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን ግን ተልዕኮዋን ሳትተው፣ ሳትጠፋ፣ የምትቀጥል ብቸኛ የእግዚአብሔር ተቋም ናት፥

· አማኝ በግል / አማኞች እንደ ማህበር ከጌታ ጋር ባላቸው ጉዞ፣ ስደት እና መከራ የመለያ ምልክታቸው ነው፥

o ስለ ጽድቅ መሰደድ፥

o በዓለም መጠላት፥

o በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰልን ለመኖር በመውደዳችን መሰደድ፥

o ስለ ክርስቶስ ስም መነቀፍ፥

“በዚያን ቀንም በኢየሩሳሌም ባለች ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ፤ ሁሉም ከሐዋርያትም በቀር ወደ ይሁዳና ወደ ሰማርያ አገሮች ተበተኑ። በጸሎትም የተጉ ሰዎች እስጢፋኖስን ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት። ሳውል ግን ቤተ ክርስቲያንን ያፈርስ ነበር፤ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጐተተ ወደ ወኅኒ አሳልፎ ይሰጥ ነበር። የተበተኑትም ቃሉን እየሰበኩ ዞሩ። ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው። ሕዝቡም የፊልጶስን ቃል በሰሙ ጊዜ ያደርጋት የነበረውንም ምልክት ባዩ ጊዜ፥ የተናገረውን በአንድ ልብ አደመጡ። ርኵሳን መናፍስት በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ከብዙ ሰዎች ይወጡ ነበርና፤ ብዙም ሽባዎችና አንካሶች ተፈወሱ፤ በዚያችም ከተማ ታላቅ ደስታ ሆነ።” የሐዋርያት ሥራ 8:1-8

ለዛሬው ጥናት አውድ፣ ዳራ እና አጭር ቅኝት፥

· የዚህ መጽሐፍ ጸሀፊው ሉቃስ ነው፣

· የተጻፈውም በ70 ዓ/ም ወይም በ80 ዓ/ም ውስጥ ነው ተብሎ ይገመታል፣

· ሉቃስ በዚህ በሐዋሪያት ስራ መጽሐፍ ውስጥ ትኩረት ሰጥቶ የሚያተኩረው፣ በመጀመሪያ መጽሐፉ “የሉቃስ ወንጌል” የተረከው እና የጻፈው በክርስቶስ የተጀመረው ስራ እና ትምህርት፥ በሐዋሪያት ሥራ በደቀ መዛሙርቱ እና ወንጌሉን በተቀበሉት ተከታዮቹ እንደቀጠለ ማሳየት ነው፣

· ይህ መጽሐፍ የተከፈለው በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች ነው፥

o መግቢያ፥ ምዕራፍ 1

o እየሩሳሌም፥ ምዕራፍ 2-7

o ይሁዳ እና ሰማሪያ፥ ምዕራፍ 8-12

o የወንጌል መልክተኝነት ጉዞ፥ ምዕራፍ 13-20

o የጳውሎስ ምስክርነት እስከ ሮም መድረስ፥ ምዕራፍ 21-28

· በዛሬው የቃል ጊዚያችን በሐዋሪያት ሥራ ምዕራፍ 8 የመጀመሪያው ስምንት ቁጥሮች ላይ በማተኮር ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰው የመጀመሪያ ብተና ላይ የተከሰቱት ክስተቶችን እንመለከታለን፣

በቤተ ክርስቲያን ላይ የተነሳ ተግዳሮትና ያስከተለው ብተና፥

· የእስጢፋኖስ አሰቃቂ ሞት፥

o እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ ሞተ! ሳውልም በሞቱ ተባባሪ ነበር፣

· የቤተ ክርስቲያን መፍረስ እና የአማኞች ወደ ወኅኒ መጣል፥

· በአማኞች ላይ የደረሰ ስደት እና መበተን፥

መከራ፣ ብተና፣ ስደት - ያላገደውና ያላጠፋው የቤተ ክርስቲያን የወንጌል አገልግሎት፥ በምን ተገለጸ . . .

· አማኞች የጌታን ፊት ይፈልጉ ነበር፥

· ቅዱሳን፥ ህብረትቸውን፣ አብሮነታቸውን እና መተባበራቸውን አላጓደሉም ነበር፥

· ቅዱሳን ቃሉን፣ ክርስቶስን ሰበኩ፣ (እውነተኛ ወንጌል)

· መንፈስ ቅዱስም፥

o ቃሉን ያጸና ነበር፣

o በድንቅ እና ተዓምርም ይገለጥ ነበር፣

o እንዲሁም አንድ ልብ መሆንን በሰዋች ውስጥ ይፈጥር ነበር፣

ለከተማ የተረፈ የወንጌል ቱርፋት፥

· እውነተኛ ወንጌል ከግለሰብ አልፎ ለከተማ ታላቅ ደስታን የሚሰጥ ነው፣

ማጠቃለያ፥

ቤተ ክርስቲያን በታላቅ መከራ፣ ስደት፣ መበተን . . . ውስጥ በነበረችበት ወቅት፥ የወንጌልን ተልዕኮ ቸል አላለችም ነበር፣ አማኞችም፥

1. በጸሎት ይተጉ ነበር፣

2. ቃሉን እና ክርስቶስን ይሰብኩ ነበር፣

3. በውስጣቸው የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ድንቅና ተአምር፣ የመንፈስም አንድነት ነበር፣

4. በውጭ ለነበሩት ሰዎችም የታላቅ ደስታ ምክንያቶች ነበሩ፣

የት ነን ያለነው?

እያለፍንበት ያለው፥ “ማንኛውም ሁኔታ” እውነተኛ ከሆነ ከወንጌል አገልግሎት እና ተልዕኮ አጉድሎናል?

Related Media
See more
Related Sermons
See more
Earn an accredited degree from Redemption Seminary with Logos.